Quantcast
Channel: Degaanka - Cakaara News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

የኢ.ሶ.ክ.መ. የክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች በመንገድ በማስተሳሰር የማህበረሠቡን ልማት ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ተገለጸ

$
0
0

ቀብሪበየህ(cakaaranews)እሮብ:ግንቦት 29/2010ዓ.ም.በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት ከቀብሪበያህ ከተማ አስተዳደር እስከ ሀርቲሼክ እየተሠራ ያለው የኮንክሪት አስፋልት መንገድ በተያዘለት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ። የክልሉን ዞኖችና ወረዳዎችን በመንገድ መስረተ ልማት ለማስተሳሰር ከሚደረገው የልማት ሥራዎች አንዱ የሆነው ከቀብሪበያህ እስከ ሀርቲሼክ ድረስ ያለውን የ23 ኪ.ሜ ርቀት በኮንክሪት አስፋልት መንገድ ለመሸፈን የተጀመረው ሥራ በታቀደለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የተናገሩት የቀብሪበያህ ሀርቲሼክ መንገድ ፕሮጀክት ኮንስትራክሽን መሃንዲስ አቶ ሳምሶን ገ/አብ ናቸው።

በዚህም አቶ ሳምሶን ገ/አብ "ሁለት ነገሮችን ነው የሠራ ነው ከጠረጋው ሥራ ጎን ለጎን የካምፕ ኮንስትራክሽንም ሥራ ነበረ በዛም ላይ የሁለቱም ጠረጋ ሥራም ሌላው ነው። ሊፈጅብን የሚችለውም ጊዜ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንጨርሳለን ብለን እናምናለን" ሲሉ ገልጿል።

በጨማሪም የመንገዱ መሠራት በአካባቢው የሚገኘውን ማህበረሠብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳደግላቸው የሚታመን ሲሆን የመንገድ ፕሮጀክቱ መጀመርም የሥራ እድል መፍጠር እንደቻለም ኃላፈው ተነግሯል። በግንቦት ወር 2010 ዓ.ም ሥራው የተጀመረው የቀብሪበያህ ሀርቲሼክ የኮንክሪት አስፋልት መንገድ ሥራው በተጀመረ በአጭር ጊዜያት ውስጥ የ5 ኪ.ሜ የጠረጋ ሥራና የመንገድ ካርታ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀም የኮንስትራክሽን መሃንዲሱ አብራርቷል።

"አሁን የደረስንበት ደረጃ  5 ኪሎሜትርን የቤንች መሙላት ሥራና የአፈር ጠረጋ ሥራ ጨርሰን  በዲዛይኑ መሠረት የሙሌት ሴክሽን ነው የመጀመሪያ ደረጃ ሙሌት በ15 ኪ.ሜ ውስጥ እየሠራን ሲሆን በቀጣይም የ5 ኪ.ሜ ጠረጋ ሥራዎችን እንሠራለን።" ሲሉ አቶ ሳምሶን ተናግሯል።

በርካታ ሥራዎች እንደሠሩ የተናገሩት የፕሮጀክት ኮንስትራክሽን መሃንዲሱ የ23 ኪሎሜትሩ የጥርጊያ መንገድ ከተጠናቀቀ በኋላ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እንደሚጀመርም አስረድቷ። የቀብሪበየህ ሀርቲሼክ የመንገድ ፕሮጀክት አንድ የኮንክሪት አስፋልት  መንገድ ሲሆን የፕሮጀክቱን ኮንትራት የወሰደውን  የኢ.ሶ.ክ. ገዢና ልዩ ኮንስተራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከመሆኑ ባሻገር የክልሉ ዲዛይንና ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ በፕሮጀክቱ ኮንስተራክሽን ስራዎች ቁጥጥርና ክትትል እንደሚያደርግም ተገልጿል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>