Quantcast
Channel: Degaanka - Cakaara News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

የቀብሪደሃር ከተማ መስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች 12 የድንጋይ ንጣፍ መንገዶች አስመርቀዋል

$
0
0

ቀብሪዳሃር (Cakaaranews) እሮብ፤ግንቦት 15/2010 .የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልላዊ መንግስት ለክልሉ ህዝብ አስፈላጊውን የመሠረተ ልማት ግንባታ በሁሉም አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል። በዚህም የክልሉ መንግሥት የመንገድ መሠረተ ልማት ችግሮችን በመቅረፍ በክልሉ የሚገኙትን ወረዳዎች እና ቀበሌዎች እርስ በእርስ በማስተሳሰር እንዲሁም ህብረተሰቡ በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ፣ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሥራዎች ላይ ትስስር እንዲኖራቸው ክልሉ የመንገድ አገልግሎት ተደራሽነትን ወደ ላቀ ደረጃ በማድረስ ላይ ይገኛል።

በመሆኑም የቀብሪዳሃር ከተማ መስተዳደር 12 ግንባታቸው የተጠናቀቀ የድንጋይ ንጣፍ (ኮብል ስቶን) መንገዶች   የቀብሪዳሃር ከተማ መስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች እንዲሁም የከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት የቀብሪዳሃር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዩሱፍ ሀሰን አስመርቋል። በምረቃት ሥነ ስርዓት ላይ የከተማው ከንቲባ አቶ ዩሱፍ ሀሰን 12ቱን የኮብል ስቶን መንገዶች ግንባታ ለማጠናቀቅ የወጣው ወጪ 9.5 ሚልዮን ብር እንደሆነ ፣ ለ520 የከተማዋ ነዋራዎችም የሥራ እድል እንደፈጠረላቸው እንዲሁም መንገዶቹም ጥራት ባለው መልኩ እንደተሠሩና ቀደም ሲል በከተማው የነበረው የመንገድ መሠረተ ልማት ችግሮችን እንደሚቀርፍም ገልጿል።

በመንገዶቹ ግንባታ የሥራ እድል የተፈጠረላቸውና በምርቃት ሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የከተማው ነዋሪዎች  በበኩላቸው በመንገዶቹ መገንባት የተሰማቸዉን ደስታ በመግለፅ ፣ የመንገዶቹ መገንባት በከተማው ህብረተሰብ የእለት ተእለት እንቅስቃሴና በአከባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ትልቅ እምርታ እንሚያመጡ አክለው ተናግረዋል።

 

 

 


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>