Quantcast
Channel: Degaanka - Cakaara News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር የከተማውን ዋና ዋና መንገዶች እድሳት እንደሚያደርግና አዳዲስ መንግዶችም እየሠራ መሆኑን ገለጸ

$
0
0

ጅግጅጋ(Cakaaranews)እሮብ፤ግንቦት 15/2010ዓ.ም የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግሥት የክልሉን ዞኖችና ከተሞች የሚያስተሳስሩ መንገዶችና ትላልቅ ድልድዮች በአፋጣኝ የሚሠራበት ፖሊሲና ስተራቴጅዎች ነድፎ በክልሉ የሚገኙ ትላልቅ ከተሞችና በዞኖች ገጠር አከባቢዎች የመንግድ መሠረተ ልማት አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

በዚህም የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዲአዚዝ መሀድ “በከተማው ዳርቻ ወይንም በቅርብ እርቀት ላይ የሚገኙ ሰፈሮች አዳዲስ የውስጥ ለውስጥ እና ረጃጅም የአስፋልት መንገዶች ግንባታ በክልሉ ኮንስትራክሽን ፣ ግዢና ልዩ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ እየተከናወኑ ነው” ብለዋል። በተጨማሪም በጅግጅጋ ከተማ የሚገኙ የ11 ፣ የ12 እና የ17 ቀበሌዎችን የሚያስተሳስር የአስፋልትና የድንጋይ ንጣፍ (ኮብል ስቶን) መንገዶች እድሳትና ጥገና እየተሠራ ከመሆኑም ባሻገር በከተማው ዳርቻ ላይ የሚገኘው የሼክ ኑር ኢሴ ሰፈርም አዲስ የአስፋልት መንገድ እየተሠራ መሆኑንም ኃላፊው ገልጿል።

በመጨረሻም በጅግጅጋ በሼክ ኑር ኢሴ መንገድ አካባቢ የሚሠሩ የታክሲ አሽከርካሪዎችና የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ባለሙያዎች የክልሉ መንግሥትና የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደሩ በከተማው ቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ ሰፈሮች አዳዲስ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በመሥራቱ ከአሁን በፊት የነበሩትን የትራንስፖርት ችግሮች እንደሚቀርፍና  የክልሉ መንግሥት ለመንገድ መሠረተ ልማት በሰጠው ትኩረት ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>