Quantcast
Channel: Degaanka - Cakaara News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

በቆለቺ ቀበሌ የሚገኙ የኢትጲያ ሶማሌ ተፈናቃይ ወገኖች የምግብድጋፍ ተደርጎላቿል

$
0
0

ቆለቺ(cakaaranews)ቅደሜ ጥቅምት 11, 2010ዓ.ም. በውሃበጤናበማህበረሰብጥናቶችና በሌሎች የመስረተ ልማትሥራዎች  ላይለሚሰሩ  ደንጀማሪያ አገር በቀል የልማት ድርጅትበዛሬ እለት በኢሶክመ አማካኝነት በባቢሌ ወረዳ ቆለቺ ቀበሌ የመልሶ ማቋቋም መጠሊያ የተደረጉለት የኢትዮጲያ ሶማሌ ተፈናቃይ ወገኖችን  የተለያዩየምግብዓይነቶችንና የቤት ማገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደርሷል

ለተፈናቃዮችሁ የተደረገለት የምግብና ቁሳቁሶች ድጋፍን የተረከቡት የኢትዮጲያ ሶማሌ ክልል መንግስት የህብረት ስራ ማህበራት ልማትና ግብይት አጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅና የክልሉ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ጃማል ኦስማን ቆረኔ እንዳሉት “ደንጀማሪያ የልማት ድርጅት የክልሉ መንግስትና ህዝብ ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖች ኑሮ እንዲሻሻልና መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ጥረት ከክልሉ ህዝብ ጎን በቆም ተምሳሌት ከመሆናቸው ባሻገር በቆለቺ ቀበሌ ለሚገኙ የኢትዮጲያ ሶማሌ ተፈናቃይ ወገኖችን  የተለያዩየምግብዓይነቶችና የቤት ማገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ ሲሰጡ ለሁተኛ ግዜ ነው ብሏል ድርጁቱ ለተፈናቃይ ማህበረሰብን ለደረጉለት እርዳታም የላቀ ምስገና አቀርቧል አቶ ጀማል::በተያያዜም በክልሉ የሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ለጋሽ ድርጅቶችና እንድሁም የክልሉ ማህበረሰብም ለተፈናቃይ ወገኖቻችን የሚደረግለት ርብርብ የበኩላቸው ድርሻ እንድወጡ ጥሪ አቀርቧል::

በሌላ በኩል የደንጀማሪያ ለጋሽ ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፉኣድ አሊ ሚሬ የክልሉ መንግስት ጥሪ ምላሽ ለመስጠትና ለተፈናይ ወገኖቻችን በዘላቂነት ለመቋቋም የበኩላችን ሃላፊት ለማውጣት በቆለቺ የሚገኙ ተፈናቃዮች የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች እንደ ሩዝ ስኳር ቦረሽ ዘይት አተር ባቄላ ብስኩትና ሌሎች አልሚ ምግቦች ነው የለገስ ናቸው ብሏል::

ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ ማህበረሰብ በኩላቸው የኢትዮጲያ ሶማሌ መንግስት በተከታታይ እያደረገልን ያለው ከፍተኛ ድጋፍ በጣም እንደተደሰቱበትና በኑሮኣቸውም ትልቅ ለውጥ ከመምጣቱን ገልፀዋል በተደጋጋሚ ግዜያት የአልሚ ምግብ ድጋፍ ላደረጉልንም የደንጀማሪያ ለጋሽ ድርጅትም እናመሰግናለን ብሏል::

በመጨረሻም የኢትዮጲያ ሶማሌመንግስትና የክልሉ ነዋሪዎች ከኦሮሚያ የተፈናቀሉ ወገኖች በዘላቂነት ለመቋቋምና  የተረጋጋ ኑሮ ለመገንባት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>