Quantcast
Channel: Degaanka - Cakaara News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

የኢ.ሶ.ክ ዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮ ከተለያዩ የዓለም አገራት መጥተው በጅግጅጋ ለሚገኙ ዲያስፖራዎች የጾም አፍጥራ ግብዣ መደረጉን ተገለጸ

$
0
0

ጅግጅጋ (cakaaranews)እሁድግንቦት 19/2010.የዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮው ያዘጋጀው የጋራ የጾም መፍቻ ዝግጅት ከተለያዩ የዓለም አገራት ወደ እናት አገራቸው በመምጣት አሁን በክልሉ ላለው የሠላም ፣ ልማት እና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የልማት ተሳታፊ በመሆናቸው የምስጋና ፕሮግራም እንደሆነም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮ ከተለያዩ የዓለም አገራት መጥተው በአሁኑ ወቅት በጅግጅጋ ከተማ ለሚገኙ የክልሉ ተወላጅ ዲያስፖራዎች በጋራ ጾም የሚፈቱበት የግብዣ ፕሮግራም ማዘጋጀቱ ገልጸዋል።

በዚህ የረመዳን ጾም በጋራ ጾማቸውን እንዲፈቱ የክብር የጾም መፍቻ ፕሮግራም ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከአሜሪካ፤ከአውሮፓ፤ከኤሲያና ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ተወላጅ የኢትዮጵያ ሶማሌ ዲያስፖራዎች ተገኝተዋል።በመድረኩ ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት በኢ.ሶ.ክ ፕሬዝዳንት የህዝብ ቅሬታ አፈታት አማካሪና የክልሉ የዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲረዛቅ ሰሃኔ ንግግራቸውን የጀመሩት ተወላጅ ዲያስፖራዎቹ እያደረጉ ባለው የሠላም ፣ የልማት ፤የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተሳትፏቸው እንዲሁም በክልሉ ባለው ዕድገት ላይ ተወላጆቹ ኢንቨስት እንዲያደርጉና እንዲያለሙ የማድረጋቸውን ትልቅ ጥረት በማድረጋቸውን አመስግኗል።  በቅድሚያ በዚህ በተቀደሰና በተባረከ የረመዳን ጾም ወቅት ከእናንተ ጋር አብረን የጾም አፍጥራ ዝግጅት ላይ በመገኘቴ በራሴና በዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮ ሥም የተሰማኝን ደስታ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ፤ ሌላው በድጋሚ ያስደሰተን ነገር ቢኖር ከተለያዩ የዓለም አገራት ይህንን ያህል ተወላጅ ዲያስፖራ በአንድ  አስተሳሰብና አላማ በሃገራቸው ባለው ሠላም እና ልማት መልካም አስተዳደር ላይ የራሳቸውን ድርሻ ለመውጣት እንዲሁም የትውልድ ሃገራቸውን ለማልማት ብሎም ለመጠየቅ በፈለጉት ጊዜ መጥተው ሊያዩን በመቻላቸውና በመፍቀዳቸው ከልብ እናመሰግናቸዋለንብሏል።

በጋራ ጾም መፍቻ ዝግጅቱ ላይ የታደሙት የተለያዩ ተወላጅ ዲያስፖራዎች የዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮው አክብሮ ይህንን ዝግጅት አዘጋጅቶ በመጥራቱ እና በማሰባሰቡ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት እያደረገ ባለውም ዘርፈ ብዙ የልማት እና የእድገት ተግባራት ላይም በቀጥታ ተሳታፊ እንደሚያደርጉ አብራርተዋል። ከእንግዶቹ መካከል ይህንን ሲናገሩ በመጀመሪያ ይህንን የመሰለ የጋራ የጾም አፍጥራ ዝግጅት ያደረጉልንን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ዲያስፖራ ማስተባበሪያ ቢሮን በራሴ እና ከተለያዩ የዓለም አህጉራት በመጡት ተወላጅ ዲያስፖራዎች ሥም ምስጋናዬን አቀርባለሁ። እኛ ተወላጅ ዲያስፖራዎች ምን ጊዜም ቢሆን በክልላችን ልማት እና የክልሉ መንግሥት ጎን እንደምንቆም ልማትንም እንደምንደግፍ ለመግለጽ እወዳለሁ ክቡራንና ክቡራት  በድጋሚ በራሴ እና በተወላጅ ዲያስፖራዎች ሥም መናገር የምፈልገው የክልሉ መንግሥት እንዲሁም የክልሉ መሪ ፓርቲ ኢሶህዴፓ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለልማቱና ለህዝቡ ተጠቃሚነት በማሰብ የሚያካሂዳቸውን ተሃድሶን እንደምንደግፈውና ለእነዚህ ሁሉ የልማት ስኬቶች ደግሞ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ናቸው በዚህም አጋጣሚ ድጋፋችንን ልንገልጽላቸው እንወዳለንብሏል።

ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና የክልሉ ተወላጅ ዲያስፖራዎቹ ዛሬ ላይ በክልሉ እየተከናወኑ ባሉ ሠላም ልማት እና መልካም አስተዳደርና እንዲሁም በክልልም ሆነ አገር ደረጃ በሚደረጉ ልማትና ኢንቨስትመንት ላይ ያላቸው ተሳትፎ በጥንካሬነት ሊጠቀስ የሚችለው የክልሉ መንግሥት በውስጥና በውጭ አገራት የሚያደርጋቸው መልካም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንደሆኑ ተገልጿል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>