Quantcast
Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት የእንሰሳትእና ከፊል እርሻ ምርምር ተቋም 132 የቴክኖሎጂ ምርምሮች ማዘጋጀቱን አስታወቀ

Image may be NSFW.
Clik here to view.
ጅግጅጋ
(Cakaaranews)አርብ፤ሰኔ 01/2010 .. የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት የእንሰሳትና ከፊል እርሻ ምርምር ተቋም በ1994ዓ.ም ከተመሰረተ ጀምሮ የክልሉ አርብቶ አደርና ከፊል አርሶ አደር ኑሮ የሚሻሽል በእንሰሳት፤በሰብል ሀብት ልማት ፣ በግብሪና መካናይዜሽንሽ እንዲሁም ሌሎች ግብሪና የሚያቶክሩ  132 የቴክኖሎጂ ምርምሮች  መከናወኑን አስታውቋል፡፡ ተቋሙ 85 በመቶ የሚሆኑ የክልሉ አርብቶ አደርና ከፍል አርሶ አደር የምግብ ዋስትናና ኢኮኖሚ  ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያከናወናቸው የምርምርና ከህብረተሰብ ጋር  የማላመድ ስራዎችን ለማጠናከር  የተለያዩ ፕሮጄክቶችን ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ስሆን ከእስዊዘርላንድ መንግስት ጋር በመተባበርም የዲጂታል የዕፅዋት ናሙና አያያዝና ዝናብ አጠር አከባቢ የሚበቅሉ  ፅዋት ለማላመድና ዚሪያዎችን ለማስፋፋት የሚያስችል ፕሮጄክቶች እያከናወነ ይገኛል፡፡

Image may be NSFW.
Clik here to view.
በክልሉ የሚገኙ በርካታ የዕፅዋት ስብስብ ናሙና በዲጂታል በሆነ መንገድ በመሰብሰብ እና ለማቆየት እንዲሁም በሀገራችን በክልሉ ብቻ የሚገኙና በማጥፋት አደጋ ላይ ያሉ እፅዋቶች
ዝሪያዎች ለማስፋፋት ተቋሙ የሚያከናወነው  የፖሮጀክት አተገባበር ከትላንትናው ዕለት በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሚስተር ደንኤል የሚመራ ልዑኳን ቡድን በተቋሙ ስራዎች ጎበኝቷል፡፡ልዑካን ቡድኑ የክልሉ መንግስት የእንሰሳት እርባታና ከፊል እርሻ ምርምር ተቋም ሀላፊዎች፣ ተመራማሪዎችና ባላዉዎች በተገኙበት መድረክ በጅጅጋ ከተማ ተገኝተው በፖሮጀክቱ እየተካናወኑ ያለው የዲጂታል የእፅዋት አያያዝን፣የዉብተክል የማላመድና ስርቶ ማሳያ እንዲሁም በተቋሙ ሰርቶ ማሳያ መዓከል እየተከናወኑ የሚገኙ የሰብል ምርምር፣ ማላመድና ቴክኖለጂ ሽግግር ስረዎችን ተዛዋዊሮ የጎብኙ ስሆን በተቀሙ ባላሙዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በጉብኝቱ የተገኙት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት የእንሰሳት እርባታና ከፊል እርሻ ምርምር ተቋም ም/ዳይሬክተር አቶ አብዱረህማን መሀመድ እንዳሉን የልዕኳን ቡዲኑ ዋና አላማ በምርምር ላይ የሚገኙ ፕፖሮጀክቶችን ተግባራዊነት ለመመልከት እንደሆነ ገልጿል፡፡

Image may be NSFW.
Clik here to view.
በተጨማሪም  ም/ዳይሬክተሩ “ዛሬ የመጠው የስዊዘርላንድ አምበሳደርና ከጀአይዜድ የመጣ ዴሊገሽ ናቸው፡፡ የጉብንቱ ዋና አላማ የእኛና ጀኣይዜድ ው የትብብር ስራ እንዲሁም ከጂአይዜድ የወሰድነው ሁለት ፖሮጀክቶች ስላሉ ለመከታተልና ለማየት ነው፡፡
እነዚህ  ሁለቱ ፖሮጀክቶች አንዱን ሀርፓሪያን ዲጂታላይዜሽን የሚባል ሲሆን ይህ ሀርፓሪያን ከ20 አመት በፊት በክልላችን የተሰበሰበ ዝርያ ወደ ዲጂታላይዜሽን ለመቀየር ነው በዚህም  ፖሮጀክቱ በጣም ውጤታማ መሆኑን አረጋግጧል። ሀለተኛ ደግሞ ወተር ፖክስ የሚባልና በድርቅና ዉሃ መቆራረጥ በሚኖርበት ወቅት የተለያዩ አትክልት ለመተክል የዝናብ ውሃ ለማጠራቀምና ዉሃን እንዲያዝ የሚንጠቀምበት ነው” ሲሉ ተናግሯል፡፡

በሌላ በኩልም የተቋሙ ተመራማሪዎች በበኩላቸው በፖሮጀክቱ እያተከናወኑ የሚገኙ የዲጂታል  ምርምርና የእፅዋት ናሙና አያያዝ ስራዎች በክልሉ የዝናብ አጠር አከባቢዎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና በዘርፉ ለሚከናወኑት የሚርምር ስራዎች የጎላ ጠቀሜታ እነደሚያበረከቱ አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ብቻ የሚገኝና በዓለም ላይ ተወዳጅ የሆነና ይእብ የተባለ እፅዋት ዝሪያ ከአሁን በፊት በአምስት ዞኖች ላይ እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን  በዶሎ ዞን ስር የሚገኙ አንዳንድ ቀበሌዎች ብቻ እንደሚገኝ እንድሁም የአከባቢው ህብረሰብ ለምግብ ፣ለቤት መስሪያና ለእንሰሳት ምግብነት ስለሚጠቀሙ በስዊዘርላንድና በጂኣይዜድ ድጋፍ የሚሰራ የምርምርና ዲጂታላይዜሽን ፖሮጀክቶች የይእብ እፅዋት ዝሪያዎች ከአደጋ እንደዳነና አሁንም በስጋት እንደሚገኝም ተመራማሪዎቹ አስረድተዋል።

 


Viewing all articles
Browse latest Browse all 131746

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>